የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት፣ ለማደስም ሆነ የጠፋባቸውን ለመቀየር ቀጠሮ ለማሲያዝ ለማንም ተቋም ሕጋዊ ውክልና አልሰጠውም ብሏል።
አገልግሎቱ አክሎም በ2017 በጀት ዓመት ለ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ዜጐች የፓስፖርት አገልግሎት መስጠቱን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቢቂላ መዝገቡ ተናግረዋል።
አክለውም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለሥራ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ የውጭ ዜጎች፣ ከዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ተሳታፊዎች ፣ ከቱሪዝም እና ከፓስፖርት አገልግሎት ከ34 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱንም ገልፀዋል፡፡
