በቻይና የሚገኝ አንድ ድርጅት 26 ሚሊዮን ዶላር ለሠራተኞቹ በቦነስ መልክ አከፋፈለ

Date:

በቻይና ሄናን ግዛት የሚገኘው ሄናን ኩዋንግሻን ክሬን የተሰኘው ድርጅት እና መሥራቹ ኩይ ፔጁን፣ ካገኙት 270 ሚሊዮን ዩዋን ትርፍ ውስጥ 180 ሚሊዮን ዩዋን (26 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር) ለሠራተኞቻቸው በቦነስ መልክ በማከፋፈላቸው በዓለም ዙሪያ መነጋገሪያ ሆነዋል።

እኤአ የካቲት 13 ቀን 2026 በተካሄደው ዓመታዊ የድርጅቱ በዓል ላይ ከ60 ሚሊዮን ዩዋን በላይ የሚሆን የጥሬ ገንዘብ ኖት በረዣዥም ጠረጴዛዎች ላይ ተደርድሮ የቀረበ ሲሆን፣ ሠራተኞች በተዘጋጀ የገንዘብ መቁጠር ውድድር ላይ በተሰጣቸው የተወሰነ ጊዜ ውስጥ የቆጠሩትን ያህል ገንዘብ በሙሉ በነፃ ይዘው እንዲሄዱ ተፈቅዶላቸዋል።

የድርጅቱ ባለቤት ከዚህ ቀደም ይሰጡ የነበሩ እንደ ማጠቢያ ማሽንና የወርቅ ጌጣጌጦችን በመተው ለእያንዳንዱ ሰው ተጨማሪ 20,000 ዩዋን የጥሬ ገንዘብ ስጦታ እንዲሰጥ ትዕዛዝ ያስተላለፉ ሲሆን፣ ድርጊቱንም የፈጸሙት የሠራተኞቻቸውን የዕለት ተዕለት የኢኮኖሚ ችግር በሚገባ ስለሚረዱ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ ያልተለመደ የቦነስ ክፍያ በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ትልቅ አድናቆትንና ቅናትን የቀሰቀሰ ሲሆን፣ ብዙዎች ድርጅቱን ለሠራተኞቹ ባሳየው አሳቢነት እያመሰገኑት ይገኛሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...