በአሪ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ1 ሺሕ በላይ ዜጎች ተፈናቀሉ

Date:

ለተፈናቃዮች የመጀመሪያ ዙር ምግብ ነክ ያልሆነ ድጋፋ መደረጉ ተነግሯል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ኮመር ቀበሌ ሐምሌ 13 ቀን 2017 ዓ.ም በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ 5 የአንድ ቤተሰብ አባላት አስክሬን ተገኝቶ የቀብር ሥነ-ስርዓት መፈጸሙን፤ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማሕበር የክልሉ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተስፋዬ ዱንዳ ተናግረዋል።

ከአደጋው ጋር በተያያዘም 1 ሺሕ 19 ነዋሪዎች ተፈናቅለው በድንኳን እና በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

በክልሉ ከሚገኙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹ ማለትም ከጎፋ፣ ወላይታና ጌዴኦ ቅርንጫፎች የተሰባሰበ ድጋፍ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በኩል በቀጥታ ለተጎጂዎቹ መቅረቡንም አብራርተዋል።

በዚህም እንደ ቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶች፣ የንጽህና መጠበቂያዎች፣ ብርድ ልብሶችና ሌሎች ድጋፎች ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች በአደጋው ለተፈናቀሉ ወገኖች መቅረባቸውን ጠቁመዋል።

አደጋው ከተከሰተበት ወቅት ጀምሮ አስክሬን በማፈላለግና አስፈላጊ ድጋፎችን በማቅረብና በማስተባበር ሰፊ ሰብዓዊ ድጋፎች ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል።

በመጀመሪያ ዙር ከተደረገው ድጋፍ ባሻገር በቀጣይ ሌሎች መሰል ድጋፎችን በቀሪ ቅርንጫፎቹና በብሄራዊ ማህበሩ በኩል ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።

በዞኑ በአደጋው ጉዳት ለደረሰባቸው ሟች ቤተሰቦች ከሚሰጠው ድጋፍ በተጨማሪ ለተፈናቀሉ ዜጎች እየተደረገ ያለው ወገናዊ አጋርነት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ተስፋዬ ዱንዳ አሳስበዋል

አሐዱ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...