በአዲስ አበባ የሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የርቀት ትምህርት እንዲማሩ መፈቀዱ ተነገረ

Date:

ህዳር 12 2018

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በአዲስ አበባ የሚገኙ የሕግ ታራሚዎችን ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል በርቀት ለማስተማር የሚያስችለኝን ፈቃድ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አግኝቻለሁ ሲል ተናግሯል፡፡

ማረሚያ ቤቱ ያገኘው ፈቃድ፤ የጤና እክል ላለባቸው፣ በማረሚያ ቤት ሥራ እየሰሩ ለመማር ለሚፈልጉ እና ዕድሜያቸው ከፍ በማለቱ በክፍል ወስጥ ተቀምጠው መማር ለማይፈልጉ ታራሚዎችን በርቀት ለማስተማር በእጅጉ ይረዳል ብሏል፡፡

በፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና መሪ ስራ አስፈፃሚ አስመራ አብደታ፤ የተገኘው የርቀት ትምህርት ፈቃዱ በማረሚያ ቤት የሚሰጠውን የትምህርት ዕድል የሚያሰፋ ነው ብለውናል፡፡

በዚህ ፈቃድ አሁን ላይ ከ2,000 በላይ የሚሆኑ የሕግ ታራሚዎች የዕድሉ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኮሚሽኑ ሰምተናል፡፡

በሌሎች የፌደራል ማረሚያ ተቋማትም ማለትም በድሬዳዋ፣ በዝዋይና በሸዋ ሮቢት ማረሚያ ማዕከል የሚገኙ የሕግ ታራሚዎች የዕርቀት ትምህርት ዕድል እንዲያገኙም ከሚመለከታቸው ጋር እንደሚሰሩ አቶ አስመራ ተናግረዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የርቀት ት/ት መማር የሚፈልጉና ከአዲስ አበባ ውጪ ባሉ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች የሚገኙ ታራሚዎች ወደ አዲስ አበባ አምጥቶ የእድሉ ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱንም ሰምተናል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...