በእስራኤል እና በአሜሪካ ጥቃት ስር የምትገኘው ኢራን ወደ እስራኤል ከምትተኩሳቸው ሚሳዔሎች በተጨማሪ በባሕረ ሰላጤው አገራት ላይ በአጸፋ የምትወስደው እርምጃ ቀጥሏል።
ኤምሬትስ: ከኢራን የተተኮሰ ሚሳዔል ተመትቶ ሲከሽፍ ስብርባሪው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ውስጥ ነዋሪ የሆነ አንድ ባንግላዲሻዊ ሠራተኛን ገድሏል።
ኳታር: የዩናይትድ ኪንግደም የባሕር ትራንስፖርት ንግድ ማዕከል እንዳስታወቀው አንድ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ከኳታር የባሕር ዳርቻ ወጣ ብሎ በሚገኝ የውሃ አካል ላይ “በሁለት ተወንጫፊዎች” ተመትቷል።
ባህሬን: የአደጋ ማስጠንቀቂያ ደወል ዛሬ ጠዋት የተሰማ ሲሆን፣ የኳታር የአገር ውስጥ ጉዳይ እና የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች “በኢራን ጥቃት የተነሳን እሳት” ለማጥፋት መሰማራታቸውን አስታውቋል።
ሳዑዲ አረቢያ: የመከላከያ ሚኒስቴሯ ዛሬ ጠዋት ሁለት ድሮኖችን እና ትናንት ሌሊት ሌሎች ተጨማሪ ድሮኖችን መትቶ ማክሸፉን አስታውቋል።
ኩዌት: የአገሪቱ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን እንዳለው በዋና ከተማዋ ባለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ የሚገኝ የነዳጅ ማከማቻዎች በኢራን ድሮኖች ዒላማ መደረጋቸውን አሳውቋል። ጨምሮም በጥቃቱ “ከፍተኛ እሳት” ተነስቶ “ከፍተኛ ጉዳት” ቢደርስም በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ተገልጿል።
