በደቡብ ወሎ የሠፈሩ ተፈናቃዮች ለረሐብ ተጋልጠናል አሉ

Date:


በተለያዩ አካባቢዎች የሚደረጉ ግጭትና ጥቃቶችን ሸሽተዉ ደቡብ ወሎ ዉስጥ የሠፈሩ ተፈናቃዮች በረሐብ እየተሰቃዩ መሆኑን አስታወቁ።

የደሴዉ ወኪላችን ኢሳያስ ገላዉ ያነጋገራቸዉ ተፈናቃዮች እንዳሉት ባለፈዉ ግንቦት ወር የመጨረሻዉን የርዳታ እሕል ከታደሉ ወዲሕ ርዳታ አግኝተዉ አያዉቁም።ተፈናቃዮቹ እስከ ግንቦት ድረስ በነብስ ወከፍ 15 ኪሎ ግራም በቆሎ ይታደላቸዉ እንደነበር ተናግረዋል።

ባለፉት 3 ተከታታይ ወራት ግን እርዳታ ባለማግኘታቸዉ ረሐብ ሥለጠናባቸዉ ለልመና በየከተማዉ እየተንከራተቱ መሆናቸዉን አስታዉቀዋል።

አንዳድ አካባቢ ረሐብ፣ በሽታና ተስፋ መቁረጥ የተፈናቃዮችን ሕይወት ማጥፋቸዉ ተዘግቧልም።የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን «ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ» ባለዉ ባካባቢዉ በሚደረገዉ ግጭት ምክንያት  ለተፈናቃዮች የምግብ ዕርዳታ ማድረስ አለመቻሉን አስታዉቋል።ደቡብ ወሎ ዞን ዉስጥ 34 ሺሕ ተፈናቃዮች በ11 መጠለያ ጣቢያዎችና ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀይጠዉ ይኖራሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...