በዶናልድ ትራምፕ በዓለ ሲመት ላይ የተገኙ አምስት ባለጸጎች ከ200 ቢሊዮን ዶላር በላይ ከስረዋል

Date:

የሪፐብሊካኑ ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሕዳር ወር ላይ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ማሸነፋቸው ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ ጥር ወር ላይ ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው ወዳጆቻቸው፣ የሀገራት መሪዎች እና ባለጸጎች በተገኙበት በይፋ በዓለ ሲመታቸው ተከብሯል።

በዚህ በዓል ላይ የተገኙ የዓለማችን ቀዳሚ ባለጸጎች በዝግጅቱ ላይ ከተገኙበት ቀን ጀምሮ ኪሳራ እያስመዘገቡ እንደሆነ ብሉምበርግ ዘግቧል።

እንደ ዘገባው ከሆነ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳድር ዋነኛ አካል የሆኑት ኢለን መስክ ብቻ ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ብቻ የ148 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ አስመዝግቧል።

እንዲሁም የአማዞን እና የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ ባለቤቱ ጄፍ ቤዞስ 29 ቢሊዮን ዶላር እንደከሰረ ተገልጿል።

የአልፋቤቱ ሰርጌይ ብሪን 22 ቢሊዮን ዶላር፣ የሜታ ኩባንያ ባለቤቱ ማርክ ዙከርበርግ አምስት ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም ፈረንሳዊው የፋሺን ኢንዱስትሪ ባለቤት በርናርድ አርናልት ደግሞ አምስት ቢሊዮን ዶላር መክሰራቸው በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።

በአጠቃላይ 17 ኩባንያዎች ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ የ1 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ኪሳራ ደርሶባቸዋል ተብሏል።

ለባለጸጎቹ የገቢ መቀነስ ምክንያት ከተባሉት ውስጥ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳድር አዳዲስ እርምጃዎች፣ ከሀገራት ጋር የገቡበት የንግድ እና ቀረጥ ውሳኔዎች እና የተወሰኑት ባለጸጎች ከአስተዳድሩ ጋር ጥብቅ ቁርኝት አድርገዋል መባሉ ዋነኞቹ እንደሆኑ ተገልጿል።

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...