በጉዲፈቻ ተወስደው በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው የመመለስ ሥራ መጀመሩን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል።
ከስምንት ዓመታት በፊት በሚኒሶታ አሜሪካ በበጎ ፍቃደኛ ኢትዮጵያዉያን የተጀመረው ንቅናቄ፣ አላማው በማደጎ የተወሰዱ ኢትዮጵያውያን የማንነት ጥያቄን ምላሽ እንዲያገኝ ማድረግ እንደሆነ ተመላክቷል።
ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያውያኑ ወደ ሀገራቸው ገብተው ኢንቨስትመንት ላይ እንዲሳተፉና ሀገራቸውን የማስተዋወቅ ስራ እንዲያከናውኑ የማድረግ ዓላምም እንዳለው ተነግሯል፡፡
ኢትዮጵያውያኑን ለመቀበል የተዘጋጀው መድረክ ከጥቅምት 7 እስከ 14 ቀን 2018 ለሰባት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ የተገለጸ ሲሆን፤ ስዊዲንን ጨምሮ በተለያዩ 15 የአለም ሀገራት የሚገኙት ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ቤት ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
