የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት ከትግራይ ክልል 189 ኩንታል ወርቅ፣ ከአፋር ክልል ደግሞ 225 ኪሎ ግራም ወርቅ ግዢ መፈጸሙ ተገለጸ።
የትግራይ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 189 ኩንታል ወርቅ ለብሔራዊ ባንከ በማስገባት ከ250 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የክልሉ ማዕድን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋዓለም ሀድጉ አስታውቀዋል።
በተመሳሳይ ከአፋር ክልል ወደ ብሄራዊ ባንክ 225 ኪሎ ግራም ወርቅ መቅረቡን ክልሉ አስታውቋል፤ ወደ ባንኩ የሚገባው የወርቅ መጠን በእጥፍ መጨመሩን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊአብዱል ኢንድሪስ ገልጸዋል።
በ2016 በጀት ዓመት 96 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መግባቱን ያስታወሱት ምክትል ኃላፊው በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመትይህ ቁጥር ወደ 225 ኪሎ ግራም ወርቅ ማሳደግ እንደተቻለ መግለጻቸውን ከፕረስ ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017 በጀት ዓመት ወደ ብሔራዊ ባንክ 4ሺህ 700 ኪሎ ግራም ወርቅ ማስገባቱን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ማስታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።
