ብሔራዊ ባንክ በ2017 ከትግራይ 189 ኩንታል፣ ከአፋር ደግሞ 225 ኪሎ ግራም ወርቅ መግዛቱ ተገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት ከትግራይ ክልል 189 ኩንታል ወርቅ፣ ከአፋር ክልል ደግሞ 225 ኪሎ ግራም ወርቅ ግዢ መፈጸሙ ተገለጸ።

የትግራይ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 189 ኩንታል ወርቅ ለብሔራዊ ባንከ በማስገባት ከ250 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የክልሉ ማዕድን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋዓለም ሀድጉ አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ ከአፋር ክልል ወደ ብሄራዊ ባንክ 225 ኪሎ ግራም ወርቅ መቅረቡን ክልሉ አስታውቋል፤ ወደ ባንኩ የሚገባው የወርቅ መጠን በእጥፍ መጨመሩን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊአብዱል ኢንድሪስ ገልጸዋል።

በ2016 በጀት ዓመት 96 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መግባቱን ያስታወሱት ምክትል ኃላፊው በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመትይህ ቁጥር ወደ 225 ኪሎ ግራም ወርቅ ማሳደግ እንደተቻለ መግለጻቸውን ከፕረስ ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017 በጀት ዓመት ወደ ብሔራዊ ባንክ 4ሺህ 700 ኪሎ ግራም ወርቅ ማስገባቱን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ማስታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...