የዩክሬን አለም አቀፍ አየር መንገድ በበረራ ፒኤስ 752 ላይ በደረሰበት ጉዳት ለተጎጂ ቤተሰብ መክፈል አለበት ሲል የኦንታሪዮ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አፅድቋል።
55 ካናዳውያን እና 30 ቋሚ ነዋሪዎችን ጨምሮ 176 ሰዎችን አሳፍሮ የነበረው አውሮፕላኑ ከቴህራን ከተነሳ በኋላ በሁለት የኢራን ሚሳኤሎች ተመትቶ ወድቋል። የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ኮርፖሬሽን ጥቃት ሊደርስብኝ ነዉ ብሎ በማሰብ አውሮፕላኑ ላይ መተኮሱ ይነገራል።
ሌላ የካናዳ ፍርድ ቤት ባለፈው አመት እንዳስታወቀው አየር መንገዱ በግጭት ቀጠና ውስጥ ወይም አካባቢ ሲነሳ ትክክለኛውን የአደጋ ግምገማ ባለማጠናቀቁ ሃላፊነት የጎደለው ነው ብሏል።
በአለምአቀፍ የሞንትሪያል ኮንቬንሽን መሰረት አንድ ቤተሰቡ እስከ 180,000 ዶላር የሚደርስ ጉዳት ሊጠይቅም ይችላል፣ እናም መጠኑ ሊጨምር የሚችለው አየር መንገዱ ቸልተኛ ከሆነ ነው።
አየር መንገዱ ለተጎጂ ቤተሰቦች የሚከፈለውን የገንዘብ መጠን ሊገድብ አይችልም፣ አየር መንገዱ የቀድሞዉን የፍርድ ቤት ውሳኔ ውድቅ አድርጎታል።
የአንዳንድ ቤተሰቦች ጠበቃ ጆ ፊዮራንቴ ውሳኔውን በደስታ መቀበላቸዉን ተናግረዋል፡፡በካናዳ ፕሬስ በታተመው መግለጫ ላይ ፊዮራንቴ “የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ውሳኔ ለቤተሰቦች ትንሽም ቢሆን ፍትህ ያመጣል” ብሏል ።
ነገር ግን ቤተሰቦች ከኢራን ካሳ እየፈለጉ ነው፣ ባለሥልጣናቱ አውሮፕላኑ በስህተት መመታቱን አምነዋል።ከአደጋው ከአምስት ዓመታት በኋላ ኢራን ለአደጋው ሙሉ ህጋዊ ሀላፊነቷን እስካሁን አልወሰደችም።
በአለም አቀፍ ህግ በኢራን ላይ ክስ እየቀረበ ሲሆን ካናዳ ግን እልባት ላይ ለመድረስ አመታት እንደሚቀረው ተናግራለች።በአደጋው ከስዊድን፣ ከዩክሬን ፣ከእንግሊዝ፣ ከጀርመን፣ ከአፍጋኒስታን እና ከኢራን የመጡ ዜጎች ህይወታቸዉን አጥተዋል፡፡
