የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠርና የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ለማረጋጋት በጀመረው መደበኛ መርሃ-ግብር መሠረት፣ ነገ ማክሰኞ 17ኛውን ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚካሄድ አስታወቀ።
በዚህ የጨረታ መርሃ-ግብር ባንኩ 70 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለጨረታ ያቀረበ ሲሆን፣ ፍላጎት ያላቸው የንግድ ባንኮች በወጣው መመሪያ መሠረት መሳተፍ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ባንኩ ይህንን በየሁለት ሳምንቱ የሚካሄድ የውጭ ምንዛሬ ሽያጭ የሚያከናውነው፣ በሀገሪቱ ያለውን የውጭ ምንዛሬ አቅርቦትና ፍላጎት ለማመጣጠን እንዲሁም የውጭ ምንዛሬ ተመን መረጋጋትን ለማረጋገጥ መሆኑ መግለፁ ይታወቃል።
