ብሔራዊ ባንክ 60 ሚሊዮን ዶላር ለጨረታ አቀረበ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ነገ ረቡዕ በሚያካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፤ 60 ሚሊዮን ዶላር ለሽያጭ ማቅረቡን አስታወቀ። በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ባንኮች የሚያቀርቡትን ዋጋ ነገ ከረፋድ አራት ሰዓት እስከ እኩለ ቀን እንዲያስገቡ ብሔራዊ ባንክ ጥሪ አቅርቧል።

ለነገ የታቀደው ጨረታ፤ ኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ስርዓት ለውጥ ካደረገች ከሐምሌ 2016 ዓ.ም. ወዲህ አምስተኛ ነው። ብሔራዊ ባንክ ባለፉት አራት ዙሮች ባካሄዳቸው ጨረታዎች፤ በድምሩ 355 ሚሊዮን ዶላር ለተሳታፊ ባንኮች አቅርቧል።

አቶ ማሞ ምህረቱ በገዢነት የሚመሩት ብሔራዊ ባንክ፤ “በየሁለት ሳምንት” ልዩነት ተመሳሳይ ጨረታ እንደሚያካሄድ ያስታወቀው ባለፈው መጋቢት ወር መጨረሻ ገደማ ነበር። በዚህ መልኩ የሚካሄደው ጨረታ እስከ 2017 በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ እንደሚካሄድ ብሔራዊ ባንክ ማስታወቁ አይዘነጋም።

በእነዚህ ጨረታዎች የሚቀርበው የውጭ ምንዛሬ መጠን፤ “በወቅቱ ያለውን የውጪ ምንዛሬ ፍላጎት በማገናዘብ” እንደሚሆን አቶ ማሞ ምህረቱ በዚሁ ወቅት ተናግረው ነበር። በዚህ መሰረት ባለፈው መጋቢት ወር መጨረሻ በተካሄደው ጨረታ 50 ሚሊዮን ዶላር ለጨረታ የቀረበ ሲሆን፤ በዚሁ ጊዜ ለአንድ ዶላር የቀረበው አማካይ ዋጋ 131.7 ብር ሆኖ ተመዝግቧል።

በተመሳሳይ መልኩ በሚዝያ ወር የመጀመሪያ ሳምንት በተካሄደ ጨረታ 70 ሚሊዮን ዶላር ለጨረታ ቀርቧል። ለአንድ ዶላር በአማካይ 131.1 ብር በቀረበበት በዚህ ጨረታ፤ በጥያቄያቸው መሰረት ለ26 ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መከፋፈሉን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል። የነገው ጨረታ ውጤት አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ይፋ እንደሚደረግ ባንኩ ገልጿል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...