ቬሮኒካ አዳነ በናይጄሪያ አሳዛኝ ነገር ገጠማት

Date:

“የሚያሳዝን ቀን ነበር በናይጄሪያ ያሳለፍኩት”

ኢትዮጵያዊቷ የሙዚቃ ኮከብ ቬሮኒካ አዳነ በመላው አፍሪካ ትልቅ ግምት የሚሰጠውን የ9ኛው የአፍሪካ ሙዚቃ ሽልማት (AFRIMA) በአሸናፊነት አጠናቃለች። ቬሮኒካ በናይጄሪያ ሌጎስ በተካሄደው በዚህ ደማቅ ስነ-ስርዓት ላይ፦“The Best Artist, Duo or Group in African Traditional Music” በሚለው ዘርፍ አህጉራዊ ተፎካካሪዎቿን በመብለጥ ድልን ተቀዳጅታለች።

ከሽልማቱ በስተጀርባ ያለው አሳዛኝ ክስተት ምንድን ነው?

ድምፃዊቷ በሽልማት ስነ-ስርዓቱ ላይ ለምን አልታየሽም ለሚሏት ደጋፊዎቿ በማህበራዊ ትስስር ገጿ በሰጠችው ምላሽ በናይጄሪያ የገጠማት ነገር አስከፊ እንደነበር እንዲህ ስትል ገልጻለች

Afrima አዋርድ ላይ ብዙ ሰው ለምን አላየንሽም የሚል ጥያቄ እየመጣብኝ ነው… ምክንያቱን መናገር ይኑርብኝ አይኑርብኝ ባላውቅም በጣም የሚያሳዝን ቀን ነበር በናይጄሪያ ያሳለፍኩት፤ ብቻ ማሸነፌ በቂ እና ከበቂ በላይ ስለነበር እሱ ብቻ እንዲገን ስለፈለኩ ዝምታን መርጫለሁ። ለዛም ነው ማንም ሰው አቀባበል እንዲያደርግልኝ ያልፈለኩት ” ብላለች።

ቬሮኒካ በቆይታዋ የገጠማትን ዝርዝር ችግር ባትገልጽም፣ ሀገሯን በድል በማስጠራት ግን ዳግም ታሪክ ሰርታለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...