ቮዳኮምና ስታርሊንክ በአፍሪካ ኢንተርኔትን ለማስፋፋት ተስማሙ

Date:

ሁለቱ ተቋማት በአፍሪካ የገጠራማ አካባቢዎች የኢንተርኔት ተደራሽነትን ለማስፋትና ለቢዝነሶች ፈጣን ኢንተርኔት ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ፈፅመዋል።

በስምምነቱ መሰረት የስታርሊንክ የሳተላይት ኢንተርኔት አገልግሎት በቮዳኮም የሞባይል ኔትዎርክ በኩል ሲሰጥ በገጠራማ አካባቢዎች ለሚገኙ ትምህርት ቤቶችና የጤና ተቋማት ፈጣን አገልግሎት መስጠት ያስችላል።

በተጨማሪ ቮዳኮም የስታርሊንክን መሳሪያዎች እና አገልግሎቶች በአፍሪካ ለሚገኙት ቢዝነሶች የመሸጥ መብት ተሰጥቶታል።

ቮዳኮም በ2030 የደንበኞቹን ቁጥር 260 ሚሊየን ለማድረስ እየሰራ ሲሆን ስምምነቱ ይኸንን ራዕይ እንዲያሳካ ያግዘዋል።

ስታርሊንክ በ25 የአፍሪካ ሃገራት እየሰራ ሲሆን ስምምነቱ ሌሎች አዳዲስ ተጠቃሚዎችን እንደሚጨምርለት ታምኖበታል።

@TikvahethMagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...