ሁለቱ ተቋማት በአፍሪካ የገጠራማ አካባቢዎች የኢንተርኔት ተደራሽነትን ለማስፋትና ለቢዝነሶች ፈጣን ኢንተርኔት ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ፈፅመዋል።
በስምምነቱ መሰረት የስታርሊንክ የሳተላይት ኢንተርኔት አገልግሎት በቮዳኮም የሞባይል ኔትዎርክ በኩል ሲሰጥ በገጠራማ አካባቢዎች ለሚገኙ ትምህርት ቤቶችና የጤና ተቋማት ፈጣን አገልግሎት መስጠት ያስችላል።
በተጨማሪ ቮዳኮም የስታርሊንክን መሳሪያዎች እና አገልግሎቶች በአፍሪካ ለሚገኙት ቢዝነሶች የመሸጥ መብት ተሰጥቶታል።
ቮዳኮም በ2030 የደንበኞቹን ቁጥር 260 ሚሊየን ለማድረስ እየሰራ ሲሆን ስምምነቱ ይኸንን ራዕይ እንዲያሳካ ያግዘዋል።
ስታርሊንክ በ25 የአፍሪካ ሃገራት እየሰራ ሲሆን ስምምነቱ ሌሎች አዳዲስ ተጠቃሚዎችን እንደሚጨምርለት ታምኖበታል።
@TikvahethMagazine
