በ2026 የዓለም ዋንጫ ከካናዳ ብሔራዊ ቡድን ጋር ታሪካዊ ስኬት ማስመዝገብ የቻለውና በቅርቡ ወደ እንግሊዙ ኖርዊች ሲቲ ያመራው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ኮከብ አሊ አህመድ፣ ለሶስት ቀናት በሚቆይ ይፋዊ ጉብኝት ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ መጥቷል።
“መነሻዬም ሆነ ታሪኬ የሚጀምረው ከዚህ ነው” በማለት ወደ ሀገሩ በመመለሱ የተሰማውን ታላቅ ኩራት የገለጸው አሊ፣ በቆይታው የተለያዩ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦችን እንደሚጎበኝ ተገልጿል።
የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሐመድ ለተጫዋቹ ደማቅ አቀባበል ያደረጉለት ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን መለያንም በስጦታ አበርክተውለታል።
የባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር እንዲህ ያሉ ስኬታማ የዳያስፖራ ልጆች ወደ ሀገራቸው መመለስ ለኢትዮጵያ ወጣቶች ትልቅ ተስፋና አርአያ እንደሚሆን የገለጸ ሲሆን፣ አሊም ወደፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ መድረክ ላይ እንደሚሳተፍ ያለውን አዎንታዊ ምኞት አጋርቷል።
በአሜሪካው MLS ባሳየው አስደናቂ ብቃት በጥር 2026 ወደ ኖርዊች ሲቲ ያመራውና ለካናዳ ብሔራዊ ቡድን 28 ጨዋታዎችን ያደረገው አሊ አህመድ፣ ይህ ጉብኝቱ በትውልደ ኢትዮጵያውያንና በሀገራቸው መካከል ያለውን ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር ታሪካዊ ክስተት ሆኖ አልፏል።
