ሕንድ በጠፈር ታሪክ ተአምር ሰራች

Date:

የሕንዱ ‘ስካይሩት ኤሮስፔስ’ ኩባንያ በሀገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያውን በግል የበለፀገ ‘ቪክራም-1’ የተሰኘ የምህዋር ሮኬት በ15 ደቂቃ ውስጥ የተሸከማቸውን ጭነቶች በ450 ኪሎ ሜትር ምህዋር ላይ በተሳካ ሁኔታ በማድረስ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፍቷል።

“የአጋማንተልእኮ” የተሰኘው ይህ ታሪካዊ በረራ፣ በዘመናዊ የ3D ህትመት ቴክኖሎጂ የተገነባ ሲሆን፥ ሕንድን በግል ድርጅት አማካኝነት ሮኬት የማስወንጨፍ አቅም ካገኙ የዓለማችን ጥቂት ሀገራት ተርታ እንድትሰለፍ አድርጓታል።

የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ይህ ስኬት የወጣቶችን ተሰጥኦና ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸው አበረታተዋል።

ይህ ስኬት ሕንድ የጠፈር ዘርፉን ለግል ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረጓ ያስገኘው ትልቅ ውጤት ሲሆን፣ መንግሥት የሀገሪቱን የዓለም አቀፍ የጠፈር ኢኮኖሚ ድርሻ በአሁኑ ጊዜ ካለው 8 ቢሊዮን ዶላር በ2033 ወደ 44 ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ ላቀደው እቅድ ትልቅ መነሻ ሆኗል።

የ1 ቢሊዮን ዶላር ግምት ያለው ስካይሩት ኩባንያ ወደ መደበኛ የንግድ በረራዎች ለመሸጋገር የተዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ሕንድ በአነስተኛ ሳተላይት ማስወንጨፊያ ገበያ ውስጥ እንደ ስፔስኤክስ ካሉ ዓለም አቀፍ ግዙፍ ተቋማት ጋር ጠንካራ ተወዳዳሪ እንድትሆን ዕድል ይሰጣታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ...

ሱልጣን ቢን ኻሊፋ ግሩፕ በኢትዮጵያ በሆቴል ዘርፍ ሊሰማራ ነው

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር...

የአሜሪካ የታክስ ህግ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ሽልማት ስጋት ላይ ጣለ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከዓለም ዋንጫ ሊያገኘው ከሚችለው 50 ሚሊዮን...

ህወሓት ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የሚደረግ ጥምረት አስፈላጊ መሆኑን ገለጸ

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ...