ትራምፕ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የሰላም ስምምነት እንድትፈጽም ከ10 እስከ 12 ቀናት ሰጡ

Date:

የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ሰላም ለመፍጠር ከ10 እስከ 12 ቀናት ብቻ እንደሚሰጧት አስጠንቅቀዋል።

ከሁለት ሳምንታት በፊት ትራምፕ የሩሲያው መሪ ቭላድሚር ፑቲን የሰላም ስምምነት እንዲያርጉ የ50 ቀናት ቀነ ገደብ ሰጥተዋቸው ነበር።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አሁን ‹‹ለመጠበቅ ምንም ምክንያት አይታየኝም››ብለዋል።

ትራምፕ ‹‹እኔ ጉዳዩ እንዲፈታ ብሞክርም እስካሁን ምንም የሰላም ንግግር ሂደቶች እየተመለከትን አይደለም›› ሲሉ ገልጸዋል።

ትራምፕ ስምምነት ላይ ካልተደረሰ በሩሲያ ላይ ማዕቀብ እና ሁለተኛ ደረጃ ታሪፍ እንደሚጥሉ ዝተዋል።

ፑቲን ጦርነቱን ስለማቆም እያወሩ በዩክሬን ሰላማዊ ዜጎች ላይ ቦምብ ማዝነባቸውን በመቀጠላቸው የሰነዘሩትን ትችት ደግመውታል።

በፕሬዝዳንት ፑቲን ቅር ተሰኝቻለሁ፤ ከእንግዲህ ለማውራት ብዙም ፍላጎት የለኝም ብለዋል፡፡

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በኤክስ ገጻቸዉ ላይ የትራምፕን ‹‹ግልጽ አቋም እና ቁርጠኝነት›› በደስታ ተቀብለነዋል ሲሉ ገልጸዋል።

የዩክሬን አየር ኃይል ፤ሰኞ ሌሊት ከ3መቶ በላይ ድሮኖች እና ሰባት ሚሳዔል በዩክሬን ላይ እንደተጣለ አስታዉቋል።

ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...