ትራምፕ በኢራን ላይ ሊሰነዝሩትየነበረውን ጥቃት በድንገት አስቆሙት

Date:

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን የኻርግ ደሴት ላይ ሊሰነዘር የነበረው ጥቃት በድንገት ‘እንደተገታ’ አስታውቀዋል። ፕሬዝዳንቱ ቀደም ሲል ኢራንን “ክፉኛ እንመታለን” ብለው ቢዝቱም፣ አሁን ግን ከኢራን ጋር የሚደረገው ውይይት ትልቅ መሻሻል ማሳየቱንና በዚህ ሳምንት አውሮፓ ውስጥ ስምምነት ላይ ሊደረስ እንደሚችል ገልጸዋል።

ይህ ስምምነት ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያግድና የሆርሙዝ ወሽመጥ በአፋጣኝ እንዲከፈት የሚያስገድድ እንደሚሆንም ትራምፕ አረጋግጠዋል። ይህንን ተከትሎም በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ መቀነሱ ታውቋል።

በሌላ በኩል የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የአሜሪካን አቋም ያስተባበሉ ሲሆን፣ አሜሪካ በድርድሩ ላይ “ከልክ ያለፈ ጥያቄ” እያቀረበች በመሆኑ ስምምነት ላይ ለመድረስ አለመቃረባቸውን ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ ሁለቱን አገራት ለማሸማገልና ውጥረቱን ለማርገብ ኳታር ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ጥረት እያደረገች መሆኑ ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...