የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሁለቱ አገራት መካከል የታሪፍ ስምምነት ላይ ለመድረስ የተቀመጠው ቀነ ገደብ ከመጠናቀቁ በፊት መግባባት ላይ የማይደረስ ከሆነ በጃፓን ላይ “30 ወይም 35 በመቶ” ታሪፍ እንደሚጥሉ ዛቱ።
ይህም በፈረንጆቹ ሚያዝያ 2 ቀን በዓለም ዙሪያ ባሉ አገራት ላይ ከፍተኛ የገቢ ቀረጥ ባወጁበት ወቅት ጃፓን ላይ ከተጣለው የ24 በመቶ ታሪፍ የበለጠ ይሆናል።
በአብዛኞቹ የንግድ አጋሮች ላይ ተጥሎ የነበረው ታሪፍ ከዋሽንግተን ጋር የሚደራደሩበት ጊዜ ለመስጠት በሚል ለ90 ቀናት ወደ 10 በመቶ ዝቅ ብሎ ነበር።
ይህ የእፎይታ ጊዜ በሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ የሚገባደድ ሲሆን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀነ ገደቡን የማራዘም ሃሳብ እንደሌላቸው ተናግረዋል።
ትራምፕ ከቶኪዮ ጋር ስምምነት ላይ መድረስ ስለመቻሉ ጥራጣሬ አላቸው የቢቢሲ ዘገባ ነው።
