ትራምፕ ካይሮንና አዲስ አበባን ማስታረቅ ይፈልጋሉ

Date:

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የዓረብ እና የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቦውሎስ እንዳሉት፤ ዶናልድ ትራምፕ በናይል ወንዝ ተፋሰስ አገሮች መካከል የውሃ አጠቃቀም ስምምነት እንዲደረስና የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውዝግብ እንዲፈታ ካይሮንና አዲስ አበባን ማስታረቅ ይፈልጋሉ።

ዋሽንግተን ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄዎችን እንደምትፈልግ እና ከሁሉም ወገኖች ጋር ንግግሮች መቀጠላቸውን የገለጹት አማካሪው፣ ግብፅና ኢትዮጵያ ሁሉንም አገሮች የሚያረካ ስምምነት ላይ ለመድረስ በውይይት እንዲሳተፉ አሜሪካ ማበረታታቷን እንደቀጠለች ተናግረዋል።

በሌላ በኩል፣ ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን በታሪካዊ የናይል ውሃ ስምምነቶች ዙሪያ ስላሉት ውዝግቦች፤ ዋሽንግተን የሦስቱ አገሮች ባለሙያዎች በጋራ በመሥራት ለተነሱት ቴክኒካዊ ችግሮች መፍትሄ እንዲያገኙ ታበረታታለች ብለዋል።

አሜሪካ ለሁሉም ወገኖች ቴክኒካዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ባለሥልጣኑ አረጋግጠዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...

«ግብጽ ዛቻውን አቁማ ወደ ድርድር ትግባ!»

ታዋቂው የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝ ዶ/ር ዴቪድ ማትሳንጋ ግብጽ በኢትዮጵያ...