አሊኮ ዳንጎቴ ከዳንጎቴ ሲሚንቶ ሊቀመንበርነት ለቀቁ

Date:

ናይጄሪያዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ከዳንጎቴ ሲሚንቶ ሊቀመንበርነት መልቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።

ይህ ውሳኔ ከዚህ ቀደም ከሌላኛው ድርጅታቸው ከለቀቁ በኋላ የመጣ ሲሆን፣ ኩባንያው የዳንጎቴ መልቀቅ አስቀድሞ ታቅዶ በነበረው የአመራር ሽግግር ሂደት አካል እንደሆነ አስታውቋል።

በአቶ ዳንጎቴ ምትክ ኢማኑኤል ኢካዞቦህ የዳንጎቴ ሲሚንቶ አዲስ ሊቀመንበር ሆነው ተሹመዋል።

ዳንጎቴ ሲሚንቶ በአፍሪካ ትልቁ የሲሚንቶ ፋብሪካ ሲሆን፣ ናይጄሪያን ከሲሚንቶ አስመጪነት ወደ ትልቁ ላኪነት በመቀየር ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።

ድርጅቱ በዓመት 48.6 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ ያመርታል።

በኢትዮጵያ የሚገኘው የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ በቅርቡ 400 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ የማስፋፊያ ፕሮጀክት እንደሚካሄድበት ተገልጿል።

ይህ መስፋፋት የፋብሪካውን የዓመት ምርት ከ5 ሚሊዮን ቶን በላይ ከማድረጉም በላይ ለተጨማሪ 25,000 ሰዎች የስራ እድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...