አሜሪካና ቻይና ለ3 ወራት ታሪፍ ላለመጨመር ተስማሙ

Date:

አሜሪካና ቻይና አቅደውት የነበረዉን የታሪፍ ጭማሪ ለ90 ቀናት ለማራዘም መስማማታቸዉ ተገለጸ፡፡ ይሄ የተሰማው ሁለቱ ሀገራት በጉዳዩ ላይ በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው።

ሁለቱ ሀገራት ከስምምነት የደረሱትም ለተጨማሪ ሶስት ወራት ታሪፍን ላለመጣል አስቀምጠውት የነበረው ቀነ ገደብ አልቆ የመጨረሻው ቀን ላይ ደርሰው ነዉ።

ሀገራቱ ከስምምነት ባይደርሱ አሜሪካ ከቻይና በምታስገባቸው ምርቶች ላይ የምትጥለውን ታሪፍ እስከ 145 በመቶ ከፍ ታደርግ የነበረ ሲሆን፤ ቻይና በአሜሪካ ላይ የምትጥለው የታሪፍ መጠን ግን አልታወቀም ነበር።

ይሁን እንጂ አሜሪካ ከዚህ በፊት በቻይና ዕቃዎች ላይ ጥላ የነበረዉ የ30 በመቶ የታሪፍ ጭማሪና ቻይናም በአሜሪካ ምርቶች ላይ የጣለችዉ የ10 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ እንደሚቀጥል ተዘግቧል።

ጋዜጣ+

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...