የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ለዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ሎተሪ ምዝገባ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ዶላር የአገልግሎት ክፍያ እንደሚጠይቅ አስታውቋል።
ይህ የማይመለስ ክፍያ ከDV-2027 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን፣ መሥሪያ ቤቱ ይህን ለውጥ ያመጣው የሎተሪውን የማስተዳደር ወጪ ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለመከፋፈል ታስቦ እንደሆነ አስረድቷል።
ቀደም ሲል የ330 ዶላር የኢሚግሬሽን ቪዛ ክፍያ የሚከፍሉት የተመረጡት ብቻ ሲሆኑ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ያልተሳኩ አመልካቾች ምንም ሳይከፍሉ ይቆዩ ነበር።
አሁን ባለው አሰራር ግን በግምት 25 ሚሊዮን የሚሆኑ ዓመታዊ ተመዝጋቢዎች እያንዳንዳቸው 1 ዶላር በመክፈል፣ ወጪው በ55,000 አሸናፊዎች ላይ ብቻ ከመውደቅ ይልቅ በእኩል እንዲሰራጭ ያግዛል ተብሏል።
ክፍያው የሚሰበሰበው ፦
- የስርዓት ማሻሻያዎችን ለመደጎም፣
- የሳይበር ደህንነትን ለማሳደግ
- የሐሰተኛና በብዛት የሚቀርቡ የተጭበረበሩ ማመልከቻዎችን ለመቀነስ ያለመ ነው።
የምዝገባው ጊዜ እንደተለመደው በተያዘዉ በጥቅምት ወር የሚጀምር ሲሆን፣ ክፍያው የሚፈጸመው በኦፊሴላዊው ድረ-ገጽ አማካኝነት በኤሌክትሮኒክ ካርዶች ብቻ መሆኑን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ አስታውቋል።
via_tikvahethiopia
