አሜሪካ ያቀረበችው የ20 ቢሊዮን ዶላር መድህን

Date:

በኢራን እና በአሜሪካ መካከል እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ የቀጣናውን የባህር ላይ ንግድ ስጋት ላይ በጣለበት በዚህ ወቅት፣ ዋሽንግተን በሆርሙዝ ሰርጥ ለሚንቀሳቀሱ የነዳጅ እና የጋዝ ጫኝ መርከቦች የ20 ቢሊዮን ዶላር የመድህን ዋስትና ማቅረቧን አስታወቀች።

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ፋይናንስ ኮርፖሬሽን (DFC) እንደገለጸው፣ ይህ ውሳኔ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የተላለፈ ሲሆን፣ ዓላማውም በጦርነቱ ስጋት ምክንያት የተረበሸውን የንግድ መርከቦች በራስ መተማመን መመለስ ነው።

በዓለም አቀፍ ደረጃ 20 በመቶ የሚሆነው የነዳጅ ፍጆታ የሚያልፍበትን የሆርሙዝ ሰርጥ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ለአሜሪካና ለአጋሮቿ መዝጋቱን ተከትሎ፣ ይህ አዲስ የመድህን ዕቅድ በመርከቦች አካል፣ በማሽነሪዎች እና በጭነት ላይ ለሚደርሱ አደጋዎች የፋይናንስ ጥበቃ በመስጠት የዓለም የኃይል አቅርቦት መቋረጥን ለመከላከል ያለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...