የመራጮች ምዝገባ ተራዘመ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአንድ ወር ሲያካሄድ የቆየውን የመራጮች ምዘገባ በሁለት ሳምንት አራዘመ። ቦርዱ ጊዜውን ያራዘመው፤ በዲጂታል እገዛ ሲከናወን በቆየው ምዝገባ በተፈጠሩ ተግዳሮቶች እና በትራንስፖርት አቅርቦት ችግር የባከነውን ጊዜ ለማካካስ እንደሆን አስታውቋል።

ምርጫ ቦርድ ባለፈው ህዳር ወር ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ፤ የመራጮች ምዝገባ ለማከናወን አቅዶ የነበረው ከየካቲት 7 እስከ መጋቢት 7፤ 2018 ነበር።

ሆኖም ቦርዱ በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ያቀዳቸውን ስራዎች “አከናውኖ መጨረስ ባለመቻሉ”፤ የመራጮች ምዝገባ መጀመሪያው በሁለት ሳምንት እንዲገፋ አድርጓል።

በቦርዱ ውሳኔ መሰረት የካቲት 26 የተጀመረው የመራጮች ምዝገባ እንዲጠናቀቅ ቀነ ገደብ የተቀመጠለት ከአንድ ወር በኋላ ነበር። ቀነ ገደቡ ከመጠናቀቁ አራት ቀናት በፊት በጠቅላላ የተመዘገበው መራጭ ብዛት 36.9 ሚሊዮን መሆኑን ምርጫ ቦርድ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ መጋቢት 24 ባሰራጨው መረጃ አመልክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...