ታዋቂው የለንደን ሳምንታዊ መጽሔት ዘ ኢኮኖሚስት ከመጋቢት 12 እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚቆየው ዕትሙ በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ የሆነ የፊት ገጽ ምስል ይዞ ወጥቷል።
በዚህ የሽፋን ምስል ላይ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወታደራዊ የራስ ሄልሜት (Helmet) ደፍተው ይታያሉ። ይሁን እንጂ ሄልሜቱ የፕሬዝዳንቱን ዓይኖች ሙሉ በሙሉ የሸፈነ ሲሆን፣ በላዩ ላይ ደግሞ ጥይቶች ተደርድረውበታል።
መጽሔቱ ለዚህ ምስላዊ ትችት የሰጠው ርዕስ “Operation Blind Fury” የሚል ነው።
ይህ ምስል ፕሬዝዳንቱ የሚከተሏቸው ወታደራዊ እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች አቅጣጫ ቢስነትን ወይም ውጤቱ ያልታሰበበት የኃይል እርምጃን የሚወክል ይመስላል።
ውድ የአዲስ ስታንዳርድ ቤተሰቦች፤ የዘ ኢኮኖሚስትን የፊት ገጽ ምስል እና ርዕስ በመካከለኛው ምስራቅ እና በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር እንዴት አገኛችሁት?
