አድማስ ዩኒቨርስቲ ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች አስመረቀ

Date:

አድማስ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች በሚሊኒየም አዳራሽ አስመርቋል።

በምረቃ ሥነሥርዓቱ ለይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቱው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሞላ ፀጋዬ ፤ ዩኒቨርስቲው ባለፉት 26ዓመታት በመደበኛና  በርቀት ትምህርት በድግሪ ፣በዲፕሎማና በሰርተፍኬት በርካታ ተማሪዎችን  በማሰልጠን ማስመረቁን  ተናግረዋል ።

ዩኒቨርሲቲው በሃገሪቱ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የሚፈለገው የተማረ  የሰው ሃይል አሰልጥኖ በማቅረብ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል ።

በዛሬው እለት ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ያስመረቀው አድማስ ዩኒቨርሲቲ  ካስመረቃቸው  ተማሪዎች  መካከል 71 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል ።

አድማስ ዩኒቨርስቲ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በሶማሌላንድና ፑንትላንድ ቅርንጫፍ ከፍቶ እያስተማረ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

ተመራቂ  ተማሪዎች በሠለጠኑበት የሞያ መስክ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...