አድማስ ዩኒቨርስቲ ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች አስመረቀ

Date:

አድማስ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች በሚሊኒየም አዳራሽ አስመርቋል።

በምረቃ ሥነሥርዓቱ ለይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቱው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሞላ ፀጋዬ ፤ ዩኒቨርስቲው ባለፉት 26ዓመታት በመደበኛና  በርቀት ትምህርት በድግሪ ፣በዲፕሎማና በሰርተፍኬት በርካታ ተማሪዎችን  በማሰልጠን ማስመረቁን  ተናግረዋል ።

ዩኒቨርሲቲው በሃገሪቱ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የሚፈለገው የተማረ  የሰው ሃይል አሰልጥኖ በማቅረብ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል ።

በዛሬው እለት ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ያስመረቀው አድማስ ዩኒቨርሲቲ  ካስመረቃቸው  ተማሪዎች  መካከል 71 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል ።

አድማስ ዩኒቨርስቲ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በሶማሌላንድና ፑንትላንድ ቅርንጫፍ ከፍቶ እያስተማረ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

ተመራቂ  ተማሪዎች በሠለጠኑበት የሞያ መስክ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን...