ኢራን ከእንግሊዝ፣ ከፈረንሳይ እና ከጀርመን ከመጡ ልዑካን ጋር በቱርክ በሚገኘው የኢራን ቆንፅላ ጄኔራል ጽ/ቤት ሁለተኛ ዙር የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ድርድር አካሂደዋል፡፡
ልዑካኖቹን የጫኑ ተሽከርካሪዎች ወደ ቆንስላው ግቢ ሲገቡ የታዩ ሲሆን፤ ውይይቶቹ በዝግ በር እየተካሄዱ ነው።
ማጂድ ታክህት ራቫንቺ እና ካዜም ጋሪባባዲ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ኢራንን ወክለዋል።
ኢራን በ2015 የኒውክሌር ስምምነት የአውሮፓ ፈራሚዎች በጠየቁት መሰረት ድርድሩን ለመቀጠል ተስማምታለች።
በተጨማሪም ፓርቲዎቹ በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ከሚደረገው ቀጥተኛ ያልሆነ ድርድር በተጓዳኝ ንግግር ለማድረግ ተስማምተዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል እንዲሁም ከአውሮፓ ወገኖች ጋር የነበረው ሰፋ ያለ የድርድር ሂደት እስራኤል ሰኔ 13 በኢራን ላይ ጥቃት ከፈጸመች በኋላ ተቋርጧልተቋርጧል።
