ኢትዮጵያ ከመስኖ ፕሮጀክቶች በአመት 43 ቢሊዮን ብር አጣች

Date:

የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ባካሄደው ጥናት መሰረት፣ የከሰምና የተንዳሆ የስኳር መስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በሚፈለገው ደረጃ ባለመስራታቸው ሀገሪቱ በየዓመቱ 43 ቢሊዮን ብር እያጣች መሆኑን ገልጿል ።

የኢንስቲትዩቱ የግብርና እና ገጠር ልማት ተመራማሪ መኮነን በቀለ (ዶ/ር) ባቀረቡት ጥናት እንዳመለከቱት፣ በእነዚህ ፕሮጀክቶች መሬት ያለማሳካት፣ በግጭትና በተለያዩ ችግሮች ስራ መቆም እንዲሁም የጥገና መጓተት ከፍተኛ የገቢ እጥረት አስከትሏል።

በተለይም የከሰም ፕሮጀክት ከታቀደው 20,700 ሄክታር ውስጥ እየለማ ያለው 2,000 ሄክታር ብቻ በመሆኑ በዓመት 10 ቢሊዮን ብር ገቢ እንዳይገኝ ሆኗል ሲል ኢፕድ ዘግቧል።

በተንዳሆ ፕሮጀክት ደግሞ ከ9 ዓመታት በላይ ስራ በመቆሙ በዓመት 33 ቢሊዮን ብር ኪሳራ እየደረሰ መሆኑንና የአሌወሮ እንዲሁም ጎዴ ፕሮጀክቶችም ሙሉ አቅማቸው ባለመስራታቸው በዓመት 5.1 ቢሊዮን እና 6 ሚሊዮን ብር ገቢ እያጣች መሆኑንም ተጠቁሟል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...