በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አዘጋጅነት ከከግንቦት 8 እስከ 10፣2017 ዓ.ም ድረስ በአዲስ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል።
ኤክስፖዉ በሚኖረዉ ቆይታ የቴክኖሎጂዉን ሥነ ምህዳር ማስፋት ብሎም በዘርፉ ትብብር ማድረግ በሚቻልበት ዐውድ ዙሪያ ዉይይቶች ይካሄዳሉ።
በሁነቱ የመጀመሪያ ቀን ውሎ የሳይበር ደህንነት መሠረተ ልማት፣ ጥበቃ እንዲሁም በዘርፉ ሊቀረፉ ስለሚገባቸዉ ችግሮች ጥልቅ ዉይይቶች ይኖራሉ።
በሁለተኛዉ ቀን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የአፍሪካን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለማሳካት ያለዉን አስተዋጽኦ የሚያመላክቱ ዉይይቶች ይካሄዳሉ። የኤክስፖዉ ተሳታፊ በሆኑ ዓለማቀፍ የዘርፉ ባለድርሻዎች መካከል የልምድ ልዉዉጦችም ይደረጋሉ፡፡
አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ከዓለማቀፍ፣ ከአህጉራዊ እና ቀጠናዊ ሁኔታዎች አንጻር የሚተነትኑ ጥናታዊ ጽሁፎች ይቀርባሉ፡፡ ሌላው የሁነቱ ድምቀት ስድስት መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር ለአጠቃላይ አሸናፊዎች የቀረበበት የሮቦቲክስ ውድድር ቀጠሮ ተይዞለታል። በዚህ ዓለማቀፍ ኤክስፖ የዘርፉ ባለሙያዎች፣ ጀማሪ የቴክኖሎጂ ተቋማት እና ፖሊሲ አዉጪዎችን ጨምሮ ከ10 ሺህ በላይ ታዳሚያን ይሳተፉበታል።
