ኢትዮጵያ የደረሰችበትን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ የምታሳይበት የ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ

Date:

በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አዘጋጅነት ከከግንቦት 8 እስከ 10፣2017 ዓ.ም ድረስ በአዲስ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል።

ኤክስፖዉ በሚኖረዉ ቆይታ የቴክኖሎጂዉን ሥነ ምህዳር ማስፋት ብሎም በዘርፉ ትብብር ማድረግ በሚቻልበት ዐውድ ዙሪያ ዉይይቶች ይካሄዳሉ።

በሁነቱ የመጀመሪያ ቀን ውሎ የሳይበር ደህንነት መሠረተ ልማት፣ ጥበቃ እንዲሁም በዘርፉ ሊቀረፉ ስለሚገባቸዉ ችግሮች ጥልቅ ዉይይቶች ይኖራሉ።

በሁለተኛዉ ቀን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የአፍሪካን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ  ለማሳካት ያለዉን አስተዋጽኦ የሚያመላክቱ ዉይይቶች ይካሄዳሉ። የኤክስፖዉ ተሳታፊ በሆኑ ዓለማቀፍ የዘርፉ ባለድርሻዎች መካከል የልምድ ልዉዉጦችም ይደረጋሉ፡፡

አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ከዓለማቀፍ፣ ከአህጉራዊ እና ቀጠናዊ ሁኔታዎች አንጻር የሚተነትኑ ጥናታዊ ጽሁፎች ይቀርባሉ፡፡ ሌላው የሁነቱ ድምቀት ስድስት መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር ለአጠቃላይ አሸናፊዎች የቀረበበት የሮቦቲክስ ውድድር ቀጠሮ ተይዞለታል። በዚህ ዓለማቀፍ ኤክስፖ የዘርፉ ባለሙያዎች፣ ጀማሪ የቴክኖሎጂ ተቋማት እና ፖሊሲ አዉጪዎችን ጨምሮ ከ10 ሺህ በላይ ታዳሚያን ይሳተፉበታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...