ኢትዮጵያ 96ኛውን የዓለም አቀፉ ኢንተርፖል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ እንድታዘጋጅ ተመረጠች

Date:

ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2028 የሚካሄደውን 96ኛውን የዓለም አቀፉ የፖሊስ ድርጅት ኢንተርፖል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉnባኤ እንድታዘጋጅ ‘በሙሉ ድምፅ’ መመረጧን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

ኢትዮጵያ የኢንተርፖልን ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ እንድታዘጋጅ የተመረጠችው በ #ሞሮኮ ማራካሽ ከተማ ሲካሄድ በቆየው 93ኛ የኢንተርፖል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ነው።

ከጉባዔው ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና ሞሮኮ የፀጥታ ትብብራቸው ለማጠናከር የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ህዳር 15 ቀን መፈራረማቸውን አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል።

ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እና የሞሮኮ ብሔራዊ ደኅንነትና የግዛት ክትትል ዋና ዳይሬክተር አብደላጢፍ ሀሙሺ ናቸው።

የስምምነቱ ዓላማ በሁለቱ አገራት የፖሊስ አገልግሎቶች መካከል ያለውን ተግባራዊ፣ መረጃዊ እና ቴክኒካዊ ትብብር በማሳደግ የጥቃት ወንጀልን፣ የተደራጀ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀልን፣ የኮንትሮባንድ መረቦችን፣ ሕገወጥ ዝውውርን እና የሳይበር ወንጀልን መዋጋት ነው ተብሏል።

ከሦስት ወር በፊት እ. ኤ.አ 2025 በነሐሴ በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ ተደርጎ በነበረው 26ኛው የኢንተርፖል አፍሪካ ሪጂናል ኮንፈረንስ ኢትዮጵያ ቀጣዩን በ2027 የሚካሄደውን 27ኛውን የኢንተርፖል አፍሪካ ሪጅናል ኮንፈረንስ እንድታዘጋጅ መመረጧን መረጃው አስታውሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሺ ጂምፒንግ ምርጥ መሪ ነው!”- ትራምፕ

አሜሪካና ቻይና ተፎካካሪ ሳይሆኑ አጋርነት ያላቸው ሀገራት ናቸው አሉ...

የአሜሪካ የፀሐይ ብርሃን ኃይል አምራቾች በኢትዮጵያ ላይ የንግድ ምርመራ እንዲደረግ ጠየቁ

በአሜሪካ የሚገኙ የፀሐይ ብርሃን ኃይል አምራቾች፣ የቻይና ኩባንያዎች የአሜሪካን...

ምርጫ ለሰላም ግንባታ

ግዮን መጽሔት :-ለኢትዮጵያ ሰላም ምርጫ አማራጭ የሌለው መንገድ ነው።...