እስራኤል ዩናይትድ ኪንግደም ለፍልስጤም እውቅና ከሰጠች ወታደራዊ ትብብር ታቋርጣለች

Date:

የእስራኤል መንግሥት እንግሊዝ በሚቀጥለው ወር ለፍልስጤም እውቅና እሰጣለሁ ማለቷን ተከትሎ እርምጃውን እንደ አንድ አማራጭ እያጤነው እንደሆነ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።

“ለንደን ጥንቃቄ ማድረግ አለባት ምክንያቱም ቢቢ [የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ] እና ሚኒስትሮቻቸው መጫወት የሚችሉባቸው ካርዶች አሏቸው። እስራኤል ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር ያላትን አጋርነት ከፍ አድርጋ ትመለከታለች፤ ነገር ግን የቅርብ ጊዜ ውሳኔዎች አጋርነቱ ጫና ውስጥ እንደገባ እና የእስራኤል መንግሥት እርምጃዎችን ለመውሰድ ከወሰነ ዩናይትድ ኪንግደም ብዙ የምታጣቸው ነገሮች አሉ” ሲል የብሪታንያ ጋዜጣ ዘግቧል።

የእስራኤል የፀጥታ ካቢኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ሃማስን ለመደምሰስ በሚል ሠራዊቱ ጋዛ ከተማን እንዲቆጣጠር ያቀረቡትን እቅድ አርብ አጽድቋል።

ካቢኔው በአብላጫ ድምጽ አምስት መርሆችን አጽድቋል፡፡ ሀማስን ትጥቅ ማስፈታት፣ 50 ታጋቾችን መመለስ፣ የጋዛን ሰርጥ ከጦር ኃይል ነፃ ማድረግ፣ የእስራኤል የጸጥታ ቁጥጥር እና ከሀማስ እና ከፍልስጤም አስተዳደር ወጪ መንግሥት መመስረት።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...