እናት ባንክ “እማዬ” የተሰኘ ቅርንጫፍ ከፈተ

Date:

#እማዬ የተሰኘው አዲሱ ቅርንጫፍ ልጆች ለእናቶቻቸው ፕሮግራሞችን በነፃ ማዘጋጀት የሚችሉበት መሆኑም ተነግሯል።

ይህ በአይነቱ የተለየ ነው የተባለለት አዲሱ ቅርንጫፍ ከባንክ አገልግሎቱ በተጨማሪ ተጓዳኝ የሆኑ ተግባራት ይከውንበታል ተብሏል።

ባንኩ “እማዬ” የሚል ስያሜ የሰጠው ይህ ቅርንጫፍ በእናትነታቸው ብዙ ዋጋ የከፈሉ ነገር ግን የልፋታቸውን ያህል ያልተነገረላቸው እናቶች ውክልና እንዲኖራቸው ታስቦ የተከፈተ ነው የተባለ ሲሆን እናት ባንክ ዛሬ የከፈተውን  ቅርንጫፉን ጨምሮ የቅርንጫፎቹ ብዛት  207 መድረሳቸውን ተናግሯል።

በተጨማሪም በእናቶች ላይ ጥናት እና ምርምር ማድረግ ለሚፈልጉ ሁሉ በቅርንጫፉ የሚሰሩበት ቦታም የተዘጋጀ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ልጆች ለእናቶች ልዩ ልዩ ፕሮግራሞችን በነፃ ማዘጋጀት የሚችሉበት ነው።

በሌላ በኩል ባንኩ ያዘጋጀው “ለእናቴ” እና “የአመቱ ድንቅ እናት” የፅሁፍ ውድድር ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም መጠናቀቁ ቢታወቅም አዲሱን “እማዬ” የተሰኘውን ቅርንጫፍ መክፈትን በምክንያት በማድረግ ለአስር ቀናት ማራዘሙን ተናግሯል።

በዚህም በአዲስ አበባ የምትገኙ እና በውድድሩ መሳተፍ ለሚፈልጉ በአዲሱ ቅርንጫፍ እንዲሁም በክልሎች ላላችሁ ተወዳዳሪዎች ስራዎቻቸውን በአካባቢያቸው በሚገኝ ቅርንጫፍ ማስገባት ትችላላችሁ ተብላችኋል።

እማዬ የተሰኘው ቅርንጫፍ ፒያሳ አቡነ ጴጥሮስ መታሰቢያ ሃውልት ትይዩ በሚገኘው የቀድሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነት እና የኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት አዲስ ህንፃ ላይ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...