ከመንግሥት ጠቅላላ የካፒታል ወጪ 2.4 በመቶ የግጭት ጉዳት መልሶ ለመገንባት ተመደበ

Date:

የፌደራል መንግሥት ያወጣው አዲስ ዓመታዊ በጀት ከፍተኛ ትኩረት ለካፒታል ወጪ መስጠቱን አስታውቋል። በአጠቃላይ 415.2 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ የተመደበ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 2.4 በመቶ የሚሆነው ገንዘብ ለግጭት ጉዳት መልሶ ግንባታ እንዲውል መወሰኑ ታውቋል።

መንግሥት ከመደበው አጠቃላይ የካፒታል ወጪ ድልድል ውስጥ፣ 10 ቢሊዮን ብር (2.4 በመቶውን) ለግጭት ጉዳት የደረሰባቸውን ንብረቶችና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ወደ ነበሩበት ለመመለስ በቀጥታ እንደሚውል አስታውቋል።

ይህ ምደባ የተደረገው፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ከዓመት በፊት ግጭት ለደረሰባቸው አካባቢዎች መልሶ ግንባታ 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ከገለጸ በኋላ ነው። በወቅቱ የተገለጸው ይህ ከፍተኛ ፍላጎት፣ የአገር አቀፍ ጠቅላላ ምርት (GDP) 20.4% የሚሸፍን መሆኑ የሚታወስ ነው።

በ2018 በጀት ዓመት ውስጥ የፌዴራል መንግሥት ለመንገድ መሠረተ ልማት በድምሩ 89.1 ቢሊዮን ብር ሲመድብ ለከፍተኛ ትምህርት ፕሮጀክቶች ደግሞ ከፌዴራል ግምጃ ቤት 40.7 ቢሊዮን ብር ለፕሮጀክቶች ማጠናቀቂያ እንደሚያወጣ ጠቁሟል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...