የፌደራል መንግሥት ያወጣው አዲስ ዓመታዊ በጀት ከፍተኛ ትኩረት ለካፒታል ወጪ መስጠቱን አስታውቋል። በአጠቃላይ 415.2 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ የተመደበ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 2.4 በመቶ የሚሆነው ገንዘብ ለግጭት ጉዳት መልሶ ግንባታ እንዲውል መወሰኑ ታውቋል።
መንግሥት ከመደበው አጠቃላይ የካፒታል ወጪ ድልድል ውስጥ፣ 10 ቢሊዮን ብር (2.4 በመቶውን) ለግጭት ጉዳት የደረሰባቸውን ንብረቶችና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ወደ ነበሩበት ለመመለስ በቀጥታ እንደሚውል አስታውቋል።
ይህ ምደባ የተደረገው፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ከዓመት በፊት ግጭት ለደረሰባቸው አካባቢዎች መልሶ ግንባታ 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ከገለጸ በኋላ ነው። በወቅቱ የተገለጸው ይህ ከፍተኛ ፍላጎት፣ የአገር አቀፍ ጠቅላላ ምርት (GDP) 20.4% የሚሸፍን መሆኑ የሚታወስ ነው።
በ2018 በጀት ዓመት ውስጥ የፌዴራል መንግሥት ለመንገድ መሠረተ ልማት በድምሩ 89.1 ቢሊዮን ብር ሲመድብ ለከፍተኛ ትምህርት ፕሮጀክቶች ደግሞ ከፌዴራል ግምጃ ቤት 40.7 ቢሊዮን ብር ለፕሮጀክቶች ማጠናቀቂያ እንደሚያወጣ ጠቁሟል።
CapitalNews
