የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት አራት ወራት ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ፣ ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ እና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች በአጠቃላይ 33.65 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው አስታወቁ፡፡
ይህም በዕቅድ ለመሰብሰብ ከተያዘው 33.72 ቢሊዮን ብር አንፃር 97 ከመቶ አፈፃፀም ያለው መሆኑን ጨምረው ጠቁመዋል፡፡
ዋና ስራ አሰፈፃሚው በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አራት ወራት ከኢነርጂ ሽያጭ ብቻ 22.21 ቢሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን ጠቁመው፤ ከዕቅዱ አንፃር 99 ከመቶ አፈፃፀም ያለው መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ኢንጅነር ጌቱ አክለውም ባለፉት አራት ወራት 153 ሺህ 973 አዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መደረጉን ጠቅሰዋል ።
በተቋማችን የዲጂታል ክፍያ ስርአትን ለማጠናከር እየተደረገ ባለው ጥረት በጥቅምት ወር በኢ-ፔይምነት ክፍያ የፈፀሙት ደንበኞች ቁጥር 95 በመቶ መድረሱንም ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
የጌጡ ተመስገንን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ 👉
@getutemesgenet
@getutemesgenet
@getutemesgenet
@getutemesgenet
