ከአቦካዶ ዘይት ኤክስፖርት 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኘ

Date:


በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ወደ ውጭ ከተላከ የአቦካዶ ዘይት ከ3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።

የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኃይሉ ዬተራ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ የኢንዱስትሪ ፓርኩ በአጠቃላይ 32 ፕሮጀክቶች ይገኛሉ። ስምንቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ወደ ፓርኩ የተቀላቀሉ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 16 ሺህ ቶን የጥሬ ዕቃ ግብዓት ወደ ፓርኩ ገብቶ እንደተቀናበረ ገልጸው፤ በዚህም ወደ ውጭ ከተላከው የአቦካዶ ዘይት ብቻ 3 ነጥብ 36 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን አመልክተዋል።

300 ሺህ ዶላር የሚያወጣ ተኪ ምርትም ለሀገር ውስጥ ገበያ መዋሉን አቶ ኃይሉ ገልፀዋል።   አጠቃላይ 137 ሺህ ለሚሆኑ አርሶ አደሮች በይርጋለም አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የገበያ ትስስር መፈጠሩን አስረድተዋል፡፡

ጋዜጣ_ፕላስ |

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...