በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ወደ ውጭ ከተላከ የአቦካዶ ዘይት ከ3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።
የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኃይሉ ዬተራ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ የኢንዱስትሪ ፓርኩ በአጠቃላይ 32 ፕሮጀክቶች ይገኛሉ። ስምንቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ወደ ፓርኩ የተቀላቀሉ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 16 ሺህ ቶን የጥሬ ዕቃ ግብዓት ወደ ፓርኩ ገብቶ እንደተቀናበረ ገልጸው፤ በዚህም ወደ ውጭ ከተላከው የአቦካዶ ዘይት ብቻ 3 ነጥብ 36 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን አመልክተዋል።
ጋዜጣ_ፕላስ |
