«በረከትን ያገኘሁት በድሆች ፀሎት ነው» የሚለው ወጣቱ ባልፀጋ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ለባቡልኸይር ድጋፍ በማድረግ ይታወቃል።
ራሱንና ጓደኞቹን በማስተባበር ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ፤ ለፆምም ሆነ ለበዓል አቅመ-ደካሞችን በመንከባከብና የበዓል ተደስተው እንዲውሉ በማድረግ በባቡልኸይር ቤተሰብ ዘንድ ይታወቃል።
በዛራው ዕለትም ወጣቱ ባለጸጋ ምረትአብ አዲስ መኪና ማርቼዲስ ቤንዝ መኪናውን ገዝቶ በምስኪኖች እና በአረጋውያን ለማስመረቅ በባቡልኸይር በተገበት ዕለት ነው ድንገተኛ የአንድ ሚሊዮን ብር ስጦታ የለገው።
ልገሳውን ወዲያውኑ በማስገባት ቃሉን የሞላው ወጣቱ ባለፀጋ ለሚስኪኖች ማድረግ ለራስ እንደማድረግ መሆኑን ተናግሯል።
ክስተቱ ታዳሚውን በእንባ ያራጨ፤ በተለይም የባቡልኸይር ተጠቃሚዎች በደስታ እንባቸው የፈሰሰበት እጅግ ልብ የሚነካ ክስተት ነበር።
የድርጅቱ መሥራችና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሀናን ሙሀሙድ የወጣቱ ባለፀጋ ድንገተኛ ስጦታ ከሚስኪኖች ጋር አስለቅሷቸዋል።
ወጣቱ ባለጸጋ ለባቡልኸይር በጎ አድራጎት 1 ሚሊየን ብር ሰጠ
Date:
