ዓመታዊ የቁልቢ ገብርኤል የንግሥ በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ ዉይይት ተካሄደ

Date:

በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከበረዉ የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል የንግሥ በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ ከቁልቢ ከተማና አጎራባች የፀጥታ አካላት ጋር የገዳሙ ኀላፊዎች ዉይይት አካሄዱ።

በውይይቱ ወቅት በዓሉን ለማክበር ወደ ስፍራው ለሚጓዙ ምዕመናን በአስተማማኝ መልኩ ሰላምና ደህንነታቸዉ ስለሚጠበቅበት ሁኔታ ንግግር ተደርጓል።

ከዚሁ ጋር የትራፊክ ፍሰቱ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ስለሚኖራቸው ኀላፊነት ተነስቷል። በውይይትና ምክክሩ ላይ የፀጥታ ሥራው ከሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ከፌደራል ፖሊስ ፣ ከኦሮሚያ ፖሊስ፣ ከድሬደዋ ፖሊስ እንዲሁም ከሐረሪ ፖሊስ ጋር በጋራ በመቀናጀት እንደሚሠራም ተገልጿል።

ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ቀደም ሲል ለኢኦተቤ ቴቪ በስልክ በሰጡት አስተያየት፣ በዓሉ ያለምንም ጸጥታ ችግር በሰላም እንዲከበር ከሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት ጋር በቂ ቅድመ ዝግጅት መካሄዱን መግለጻቸው ይታወሳል።

Via የመንበረ ፓትርያርክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...