ኢትዮጵያ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እንድታስተናግድ ፍላጎት አለን

Date:

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን ኢትዮጵያ ታላላቅ የአትሌቲክስ ውድድሮችን የማዘጋጀት ፍላጎት እንዳላት ተናግሯል፡፡

በአፍሪካ ከ18 እና 20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ውድድር ላይ ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ የእውቅና እና ሽልማት መርሃ-ግብር በተካሄደበት ወቅት መልዕክት ያስተላለፈው ፕሬዝዳንቱ

’’ኬንያ የ2029 ወይም 2031 የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የማስተናገድ ፍላጎት እንዳላት አሳውቃለች ፤ እኛም በዚህ ደረጃ መፎካከር እንፈልጋለን ፤ አሁን ጥሩ ተስፋዎች አሉ ፤ አደይ አበባ ስታዲየም በጥሩ መንገድ እየተሰራ እንደሆነ እናውቃለን ፤ በተያዘለት ጊዜ ከተጠናቀቀ ትልልቅ ውድድሮችን ማዘጋጀት እንችላለን ፡፡’’ ሲል ተናግሯል፡፡

የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ እንድታዘጋጅ ንግግር መጀመሩንም ኮማንደር ስለሺ አያይዞ ጠቁሟል፡፡ ’’አሁን ላይ ተስፋ እያየን ነው፡፡ የስፖርት ማዝወተሪያ ስፍራዎች በፍጥነት እንደሚጠናቀቁ በማመን ለአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ውድድር እንድናዘጋጅ የሚያስችል ጥያቄ አቅርበናል፡፡’’ በማለት ገልጿል፡፡

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻፒዮናን 2000 ዓ.ም ላይ ማዘጋጀቷ ይታወሳል፡፡ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ በአፍሪካ ተከናውኖ አያውቅም፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...