የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ/የኢትዮጵያ ጥናት እና ምርምር ተቋም ከባህል እና ስፖርት ሚ/ር፤ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ጋር በመተባባር ዐርብ የካቲት 13 ቀን ከጠዋቱ 3 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ራስ መኮንን አዳራሽ የግማሽ ቀን ዐውደ ጥናት አዘጋጅቷል፡፡
ከኢትዮጵያ ምድር አልፎ ለአፍሪካ፣ ለአፍሪካ አሜሪካውያን፣ መላው ጥቁር ሕዝብና ለሰው ልጆች ሁሉ ኢትዮጵያውያን አርበኞች፣ አባቶቻችንና እናቶቻችን የነጻነትን ውድ ዋጋ እና ሰው የመሆን ታላቅ የመንፈስ ክብርንና ልእልናን ከፍ ያደረጉበትን የካቲት 12 የሰማዕታትቀንን ለመዘከር በተዘጋጀው ዐውደ-ጥናት ላይ በክብር እንድትገኙ ተጋብዘዋል፡፡
ቦታ፡- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፤ ራስ መኮንን አዳራሽ
ቀንና ሰዓት፡- ዐርብ የካቲት 13 ቀን ከጠዋቱ 3 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት፤
