የኢትዮጵያ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን የመድረክ ቆይታ የሚተርከውን በጋዜጠኛና መድረክ መሪ ወንድወሰን ከበደ የተዘጋጀው”የመድረክ ማስታወሻ “መጽሐፍ እሁድ ግንቦት 3/2017 በሒልተን ሆቴል በታላቅ ድምቀት ይመረቃል ።
በዝግጅቱ ላይ ስመጥር ሙያተኞች በመድረኩ ላይ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
በመድረክ ማስታወሻ የመጽሐፍ ምርቃት ሥነሥርዓት ላይ ለመድረክ ዝግጅት የተጋበዙ የሚዲያ ባለሙያዎች ዓለምነህ ዋሴ፣ ደረጀ ኃይሌ፣ አዳነች ወልደገብርኤል ፣ አንዱዓለም ተስፋዬ፣ ሰርፀ ፍሬስብሀት፣ ጥበቡ በለጠ፣ እናትፋንታ ውቤ፣ ለዓለም አሰፋ ይገኛሉ።
እንዲሁም
ከአክሱማይት ባንድ ጋር ፀጋዬ እሸቱ፣ መሳፍንት አወቀ፣ ህብስት ጥሩነህ፣ አሰግድ ሙሉጌታ፣ ግዛቸው ተሾመ፣ ዳን አድማሱ…. ይሰየማሉ
