የሮተሪ ኢንተርናሽናል ፕሬዚዳንት  የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከልን ጎበኙ

Date:

የሮተሪ ኢንተርናሽናል ፕሬዚዳንት  ዶ/ር ፍራንስኮ አሪዞ በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከልን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም ወቅት በሮተሪ ኢንተርናሽናል አማካይነት ሕክምና ካገኙ ታካሚዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።

በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከል የሚሰጠውን አገልግሎት እንዲያከናውን ድጋፍ ከሚያደርጉ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው ሮተሪ ኢንተርናሽናል፣ ከ1955 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ረዥምና ንቁ ተሳትፎ ሲያደርግ መቆየቱ ተገልጿል፡፡

ሮተሪ ኢንተርናሽናል በጤናው ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ በተለይም በበሽታ መከላከል፣ በእናቶችና ሕጻናት ጤና እና በንጽሕና አጠባበቅ (Sanitation) ዘርፎች ላይ እየሰራ እንደሚገኝ ተነግሯል።

በአሁኑ ወቅትም በኢትዮጵያ 21 የሮተሪ ክለቦች እንዲሁም የሮተሪ እና ኢንተርአክት (Interact) ክለቦች ያሉት ሲሆን፣ እነርሱም ከኢትዮጵያ የጤና ሚኒስቴርና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመተባበር በትልቅ ደረጃ የጤና ፕሮጀክቶችን ለመፈጸም እየሰሩ እንደሚገኙም ነው የተገለጸው።

በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከል ላለፉት 36 ዓመታት ከ9 ሺሕ በላይ ለሆኑ ታካሚዎች የነጻ የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎቶችን ሲሰጥ የቆየ አገር በቀል ለትርፍ ያልተቋቋመ ተቋም ነው። ተቋሙ ከሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ለሚመጡ ሁሉንም ያካተተ የልብ ሕክምና አገልግሎት ከክፍያ ነጻ በሆነ መልኩ በመስጠት ላይ ይገኛል::

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...