የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

Date:

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን ሊያደርጉ ያቀዱትን የሰላም ንግግር በበጎ እንደሚቀበሉ ገልጸው፤ ሁለቱም ወገኖች “በቅን ልቦና” ወደ ድርድር እንዲገቡ አሳሰቡ።

በመንግሥታቱ ድርጅት የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ንግግር ያደረጉት የዋና ጸሐፊው ቃል አቀባይ ስቴፋን ደዣሬክ፤ ጉቴሬዝ “ሁሉም ወገኖች ይህንን የዲፕሎማሲ እድል በመያዝ ወደ ዘላቂ እና አጠቃላይ ስምምነት ለመድረስ በቅን ልቦና እንዲሳተፉ” መጠየቃቸውን ገልጸዋል።

ዋና ጸሐፊው፤ ንግግሩ ውጥረቱን “የማርገብ እና ወደ ግጭት እንዳይመለስ የመከላከል” እድል እንደሚሰጥም አስታውሰዋል።

“ዋና ጸሐፊው፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተርን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ሕግጋት መሠረት ከሰላማዊ አማራጭ ውጪ ዓለም አቀፍ አለመግባባቶችን ለመፍታት የሚያስችል ተጨባጭ አማራጭ እንደሌለ አጽንኦት ሰጥተዋል” ሲሉ ቃል አቀባዩ ደዣሬክ ተናግረዋል።

የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የግል ልዑክ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን ለማገዝ ቀጣናው ውስጥ እንደሚገኙም ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...