የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

Date:

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን ሊያደርጉ ያቀዱትን የሰላም ንግግር በበጎ እንደሚቀበሉ ገልጸው፤ ሁለቱም ወገኖች “በቅን ልቦና” ወደ ድርድር እንዲገቡ አሳሰቡ።

በመንግሥታቱ ድርጅት የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ንግግር ያደረጉት የዋና ጸሐፊው ቃል አቀባይ ስቴፋን ደዣሬክ፤ ጉቴሬዝ “ሁሉም ወገኖች ይህንን የዲፕሎማሲ እድል በመያዝ ወደ ዘላቂ እና አጠቃላይ ስምምነት ለመድረስ በቅን ልቦና እንዲሳተፉ” መጠየቃቸውን ገልጸዋል።

ዋና ጸሐፊው፤ ንግግሩ ውጥረቱን “የማርገብ እና ወደ ግጭት እንዳይመለስ የመከላከል” እድል እንደሚሰጥም አስታውሰዋል።

“ዋና ጸሐፊው፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተርን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ሕግጋት መሠረት ከሰላማዊ አማራጭ ውጪ ዓለም አቀፍ አለመግባባቶችን ለመፍታት የሚያስችል ተጨባጭ አማራጭ እንደሌለ አጽንኦት ሰጥተዋል” ሲሉ ቃል አቀባዩ ደዣሬክ ተናግረዋል።

የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የግል ልዑክ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን ለማገዝ ቀጣናው ውስጥ እንደሚገኙም ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...