የቱርኩ ፕሬዚዳንት  ወደ  ኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉዞ ተራዝሟል ?

Date:

የቱርኩ ፕሬዚዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ቀጥሎም ወደ ኢትዮጵያ እንደሚያመሩ ተገልጾ ነበር።

በወጡት ሪፖርቶች ፕረዚደንቱ  ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ መሐመድ ቢንዛይድ የጤና ሁኔታ ጋር ተያይዞ ተራዝሟል። ሁለቱ የሀገር መሪዎች በስልክ ውይይት ማድረጋቸውም ነው የተገለጸው።

ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉዞስ ?

የቱርክ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ፕረዚዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉዞ እንደተጠበቀ ነው ሲል አስታውቋል።

ፕረዚዳንቱ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ግብዣ ወደ አዲስ አበባ እንደሚጓዙ የገለጹት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ ቡርሃኔትን ዱራን ውይይቶቹ በሁለትዮሽ ግንኙነቶች እንዲሁም በክልላዊ እድገቶች ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ድርድር የተጠናቀቀባቸው እንደ ንግድ፣ የመከላከያ የተለያዩ  መሠረተ ልማቶች ላይ ስምምነቶች እና ሰነዶች እንደሚፈረሙ ይጠበቃል ሲሉም አክለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ውጭ ምንዛሪ የሚያድኑ የሴራሚክ ምርቶች በቅርቡ ለገበያ ይቀርባሉ

ይህ የተገለፀው ኢትዮደር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በ”Golden Tier...

የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ተገለጠ

በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና አቅርቦት ላይ ተፈጥሮ የነበረው ስጋት...

አሜሪካ የኢራንን የጭነት መርከብን መያዟን አስታወቀች

በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን የዘጋችው...