የቻይና አምባሳደር ከኦሞቲክ መስራች አቶ ኢያሱ ጋር ተወያዮ

Date:

በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሀይ የተመራ የኢንቨስተሮች ልዑክ ከኦሞቲክ ግሩፕ መስራችና ባለቤት እንዲሁም ከአፍሪካ ቦክስ ኮንፌደሬሽን ፕረዝዳንት ከሆኑት አቶ ኢያሱ ወሰን ጋር ተወያዩ።

‎በቻይና አምባሳደር ቺን ሀይ የተመራው ልዑክ አርባምንጭ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የክልል እና የዞን የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የሁለትዮሽ የስራ ስምምነት ላይ ተወያይተው ተፈራርመዋል።


ከልዑኩ ጋር በሆቴል፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ በግብርና እና አግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንቨስትመንት የሁለትዮሽ ትብብር ላይ የተወያዩት አቶ ኢያሱ ወሰን ፤ ኢንቨስተሮቹ ጋር በጋራ ለማልማት ከስምምነት ደርሰዋል።

በጋሞ ዞን እና በጠቅላላው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን እና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለልዑኩ ያስረዱት አቶ ኢያሱ “በርካታ ኢንቨስትመንቶች ላይ በመሰማራት አከባቢውን ማልማት እና ግዙፍ የስራ ዕድል መፍጠር እንችላለን” ሲሉም ገልፀዋል።


‎አምባሳደር ቺን ሀይ እና የቻይና ባለሀብቶቹም ከአቶ ኢያሱ ወሰን እና መሰል ባለሀብቶች ጋር መስራት የሚችሉበት የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ በመመያየት ፍላጎታቸውን ገልፅው በቀጣይ ጥናቶችን በማድረግ ወደ ስራ የሚገቡበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ከስምምነት ተደርሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...