የነቢዩ መሐመድ መውሊድ (ልደት) ነገ ይከበራል

Date:

ሐሙስ ነሐሴ 29 2017 ዓ.ም የሚከበረውን የመውሊድ በዓል አስመልክቶ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሥራ አስፈፃሚ አባልና የወጣቶችና ሴቶች ዘርፍ ተጠሪ ሼህ አብድልሃሚድ አህመድ፤ መውሊድ ሲከበር የአካባቢን ሰላም በማስጠበቅና የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ሊሆን እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

የታላቁ አንዋር መስጊድ ኢማም ሼህ ጠሃ መሐመድ ሃሩን በበኩላቸው፤ ” ነቢዩ መሐመድ ለዓለም ሰላምና ለሰው ልጆች እዝነት የተላኩና የሰሩ በመሆናቸው ሙስሊሙ ማህበረሰቡ አርዓያነታቸውን ሊከተል ይገባል” ብለዋል።

በመውሊድ በዓል አከባበር ወቅት የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚካሄዱና በዓሉ የእስልምና አስተምህሮን ለእምነቱ ተከታዮች ለማስረፅ እንደሚረዳም ገልጸዋል፡፡

በዓሉ ነገ ሐሙስ በመላው ኢትዮጵያ የሚከበር ሲሆን፤ በአዲስ አበባም በታላቁ አንዋር መስጊድ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እንደሚከበርም ተጠቁሟል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...