የነጻነት ወርቅነህን ሕጋዊ የቤተሰብ ተወካይን ስለ ማሳወቅ

Date:

በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ሕልፈት ምክንያት ሐዘናችንን ሐዘናችሁ በማድረግ ላፅናናችሁን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። የአርቲስት ነፃነት ቤተሰብ ወደመጡበት ሃገር ከመመለሳቸው በፊት ለቤተሰቡ የቅርብ ሰዎች ሕጋዊ ውክልና ሰጥተዋል ።

በመሆኑም ፣ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህን የተመለከቱ ማናቸውንም የሥራ ጉዳዮች እንዲከታተሉና እንዲያስፈጽሙልን በማለት አቶ አስናቀ ንጉሴን የወከልን መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን።

ከአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ስም ጋር በተያያዘ ማንኛውም ጉዳይ ቢኖራችሁ አቶ አስናቀ ንጉሴን ማነጋገር እንደምትችሉ እንገልፃለን።

ከዚህ በተጨማሪም ፣ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ እና ቤተሰቡን የተመለከተ የትኛውንም ዓይነት መረጃ ማግኘት ስትፈልጉ ተወካዩን በአካል ወይም በስልክ ማነጋገር ትችላላችሁ። በተለይ የሟችንም ሆነ የቤተሰቡን ስም የሚያጠፉ እንዲሁም ክብር የሚያጎድፉ ስሁት ትርክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ እንዳይዘዋወሩ ለማስቀረት እንዲቻል ፣ ትክክለኛ መረጃዎችን ከሕጋዊ ተወካያችን ብቻ እንዲቀበሉ ፤ የተወካያችንን ቃል ብቻ ጠቅሰው እንዲጠቀሙ እንጠይቃለን።

ከዚህ ውጭ በሆነ መንገድ የሟችንም ሆነ የቤተሰቡን መልካም ስም የሚያጎድፍ ስሁት የፈጠራ ታሪክ ማሰራጨት በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑንም እናስታውሳለን።

ስልክ :- 0903886870 ( አስናቀ ንጉሴ )

ቤተሰቡ

SHARE በማድረግ መልዕክቱን እንድታዳርሱልን እንጠይቃለን

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...