ጎግል የድምፅ እገዛ መተግበሪያው ጎግል አሲስታንት የሰዎችን ንግግር ያደምጣል በሚል በካሊፎርንያ ፍርድ ቤት ቢከሰስም፣ አሁን 68 ሚሊየን ዶላር በመክፈል ክሱን ለማቋረጥ መስማማቱ ተነግሯል።
በክሱ መተግበሪያው ያለ ሰዎች ፈቃድ እንደሚሰራና የሰዎችን ንግግር እንደሚያደምጥ እና ንግግሮቹን ወደ ጎግል እንደሚልክ ተመላክቶ ነበር።
ጎግል ክሱን ለማቋረጥ 68 ሚሊየን ዶላር ለመክፈል መስማማቱን ሲገልፅ፣ የአሜሪካ ዳኛ ስምምነቱን እንዲያፀድቁት ግን ይጠበቃል ተብሏል።
በተመሳሳይ ከሳምንታት በፊት የአፕሉ ሲሪ ተመሳሳይ የሰዎችን ንግግር ያደምጣል የሚል ክስ ተከፍቶበት 95 ሚሊየን ዶላር በመክፈል ክሱን ለማቋረጥ መስማማቱ ይታወሳል።
መረጃው ከአናዶሉ የተገኘ ነው። tikvahethmagazine
