የአቶ አማን ፍስሐ ጽዮን ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

Date:

በኢትዮጵያ የሚዲያ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የከፈቱት እና የኢቢኤስ ቴሌቪዥን መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት የአቶ አማን ፍስሐ ጽዮን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ሐሙስ የካቲት 12 2018 ዓ .ም ተፈጽሟል።

ቀደም ሲል በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተከናወነው የክብር ሽኝት መርሐ-ግብር ላይ የቤተሰብ አባላት የአቶ አማንን መልካም አባትነት እና ለቤተሰባቸው የነበራቸውን ጥልቅ ፍቅር የሚዘክሩ ልብ የሚነኩ ንግግሮችን አድርገዋል።

የሃይማኖት አባቶች አቶ አማን በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ሁሉም እምነቶች በእኩልነት ለተከታዮቻቸው አስተምህሮታቸውን መንገድ የከፈተ ሚዲያ እንዲሆን ማስቻላቸውን መስክረዋል።

በተለይም በኮቪድ 19 ወቅት ከእምነት ተቋማት ጋር የሠሩት ሥራ ሲያስመሰግናቸው እንደሚኖር ነው የገለጹት።

ባለትዳር እና የሦስት ልጆች አባት የነበሩት አቶ አማን ፍስሐ ጽዮን ከቤተሰብ ኃላፊነታቸው ባሻገር፣ በሚሊዮኖች ዘንድ ተወዳጅ የሆነውን ኢቢኤስን በመመሥረት ለሀገራቸው ተወዳጅ የሚዲያ ውጤት ያበረከቱ ታታሪ መሪ እንደነበሩ ይመሰከርላቸዋል።

የአቶ አማን ፍስሐ ጽዮን ሥርዓተ ቀብር በአዲስ አበባ የቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ የሥራ ባልደረቦቻቸው እና በርካታ የጥበብ ሰዎች በተገኙበት ተፈጽሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...