የአውሮፓ ህብረት ለአፍሪካ የ58.4 ቢሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግ ነው

Date:

የአውሮፓ ህብረት ለ2028-2034 ባለው ጊዜ ውስጥ ለውጭ ሀገራት ተግባራት ከተመደበው ጠቅላላ በጀት ውስጥ ትልቁን ድርሻ ለአፍሪካ ለመስጠት ማቀዱን አስታውቋል።

የቀረበው ረቂቅ በጀት እንደሚያሳየው፣ አፍሪካ 58.4 ቢሊዮን ዩሮ (68.35 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) የገንዘብ ድጋፍ ልታገኝ ነው።

ይህ የገንዘብ ድጋፍ የህብረቱን የውጭ ጉዳይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ አንድ ነጠላ መሣሪያ ለማዋሃድ በታቀደው “ግሎባል አውሮፓ” (Global Europe) በሚባለው አዲስ ፕሮግራም በኩል የሚሰጥ ነው።

የአውሮፓ ህብረት የገንዘብ ድጋፉን በዋናነት ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና የአካባቢ ኢኮኖሚን ለማሳደግ እንደሚጠቀምበት ገልጿል። ይህም ከኢኮኖሚ ውድቀት እና ሥራ አጥነት የሚመነጨውን ሕገወጥ ስደት ለመቀነስ ያለመ መሆኑን ቅዳሜ ገበያ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል ።

KGEthiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...